ዜና(News)

ሁለቱም የግፍ እስረኞች ለ ታህሳስ 19 ተቀጠሩ
የባልደራስ ፓርቲ አባል የሆኑት የግፍ እስረኞች አቶ ካሱ ደስታና አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ ዛሬ በአራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል። በዚህም መሰረት:- በትናንትናው ዕለት (13/04/2015ዓ.ም) አቶ ካሳሁን ደስታ በአራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት መቅረባቸው ይታወሳል። ችሎቱም የፖሊስን መዝገብ ለመመርመር ለአዳር ቀጥሮ ነበር። ፖሊስ ባቀረበው መዝገብ የሶስት ሰዎች ቃል የተቀበለ መሆኑን ገልጿል።ችሎቱ በትላንትናው እለት ፖሊስ የጠየቀውን 14 ቀናት More/ተጨማሪ…

የግፍ እስረኛው አቶ ካሳሁን ለይደር ተቀጠሩ
በሀሰት ክስ ለታሰሩት አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ ስንቅ ለማቀበል እና ለመጠየቅ በሄዱበት በፖሊስ ታግተው እዛው የቀሩት አቶ ካሳሁን ደስታ ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ በቀጠሯቸው መሰረት ፍ/ቤት ቀርበዋል።ፓሊስ በዛሬው ችሎት ላይ አቶ ካሳሁን ሌላውን እስረኛ አቶ ናትናኤልን ለመጠየቅ በሄዱበት እንዳሰራቸው ክዷል። ይባስ ብሎም አቶ ካሳሁንን ያሰረበትን ምክንያት ሲናገር ”በአምሀ ደስታ ት/ቤት በነበረው ተቃውሞ ላይ ከኋላ መኪና ይዘው ሲያስረብሹ More/ተጨማሪ…
የግፍ እስረኞቹ አቶ ካሳሁን ደስታ እና አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ ነገ እና ከነገ ወዲያ ፍ/ቤት ይቀርባሉ
በግፍ እስር ላይ የሚገኙት የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ጉዳይ አስፈፃሚ እና ንቁ ተሳታፊ የሆኑት አቶ ካሳሁን ደስታ ባለፈው ታህሳስ 06/2015 ዓ.ም ፍ/ቤት መቅረባቸው ይታወሳል። ችሎቱም ተጨማሪ 7 ቀናትን ሰጥቶባቸው ነበር። በዚህም መሰረት ነገ ሀሙስ 13/04/2015 ዓ.ም በአራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት የሚቀርቡ ይሆናል። ሌላው በግፍ እስር ላይ የሚገኙት የባልደራስ የምክር ቤት አባል እና ንቁ ተሳታፊ የሆኑት More/ተጨማሪ…

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ ዞን ሚዢጋ ወረዳ ታንካራ ቀበሌ በኦሮሚያ ልዩ ኃይል ከተገደሉት ንፁሃን መካከል የሰባቱ ሰዎች አስከሬን ስርዓተ ቀብር ተፈፀመ
የኦሮሚያ ክልል ልዩ ኃይሎች የምስራቅ ወለጋ አጎራባች በሆነው በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ ዞን ሚዢጋ ወረዳ ታንካራ ቀበሌ ታህሳስ 01/2015 ዓ/ም ከረፋዱ 4 ሰዓት ጀምሮ የኦሮሚያ ልዩ ኃይሎች በከፈቱት ተኩስ በርካታ ሰዎች የተገደሉ ሲሆን የሰባቱን ሟቾች አስከሬን ብቻ መቅበር ተችሏል፡፡ በሀይል ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የገቡት የኦሮሚያ ፀጥታ ኃይሎች በወሰዱት እርምጃ የተገደሉ ህፃናት፣ሴቶችና አዛውንቶች አስከሬን በየጫካው ወድቆ More/ተጨማሪ…