ዜና(News)
በአቶ እስክንድር ነጋ ላይ ስለተፈጸመው ከባድ ድብደባ ጠቅላይ አቃቤ ህግ አስቸኳይ ማብራሪያ እንዲሰጠን እንጠይቃለን!!!
በግፍ እስር ላይ የሚገኙት የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ (ባልደራስ) ፕሬዚደንት አቶ እስክንድር ነጋ በሚኖሩበት ቂሊንጦ ወህኒ ቤት ውስጥ ጥቅምት 11/2014 ዓ.ም. ንጋት 12፡20 ደቂቃ ላይ ከፍተኛ ድብደባ ተፈጽሞባቸዋል፡፡ ከአቶ እስክንድር ነጋ ጋር አብረው በእስር ላይ ያሉት የፓርቲው የአደረጃጀት ጉዳዮች ሓላፊ አቶ ስንታየሁ ቸኮል ጥቅምት 11 ቀን 2014 ዓ.ም. በነበረው የፍርድ ቤት ቀጠሮ የተገኙ ሲሆን የባልደራስ More/ተጨማሪ…

መረጃ ! በእስክንድር ነጋ ላይ በማረሚያ ቤት ድብደባ ተፈጽሞበታል
በእስክንድር ነጋ ላይ በማረሚያ ቤት ድብደባ ተፈጽሞበታል ። በዚህም ምክንያት ጉልበቱ መቁሰሉን ዋና ሳጅን መስፍን ይልማ የተባሉ የቂሊንጦ ወህኒ ቤት የፈረቃ ሓላፊ ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል! በዛሬው ዕለት እስክንድር ነጋ ችሎት መቅረብ አልቻለም ።ይህም በመሆኑ በተከታታይ ምስክር የመስማት ቀጠሮ ተሰርዞ ፤ ለፊታችን ሰኞ ጥቅምት 15 ቀን 2014 ዓ.ም ተዘዋውሯል።ከዚሁ ጋር በተያያዘ ችሎት ለመታደም የተገኙ በጅምላ ታፍሰው More/ተጨማሪ…

ነገም እንደዛሬው የሞራል ግዴታችንን እንወጣ!
በዛሬው የእነ እስክንድር ነጋ ችሎት ላይ ለመታደም የፍርድ ቤቱ ቅጥር ግቢ ድረስ መጥታችሁ ‘አዳራሽ ሞልቷል’ በሚል ችሎቱን ሳትታደሙ የተመለሳችሁ የፍትሕ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ተቆርቋሪዎች በርካቶች ናችሁ። ከኅሊና እስረኞች ጎን መሆናችሁን ስላሳያችሁን በእጅጉ እናመሰግናለን።ችሎቱን የታደማችሁም ሆነ የተከለከላችሁ አጋርነታችሁን አሳይታቸሰኋልና ፈጣሪ አጋር ይሁናችሁ። የሞራል ግዴታችሁን መወጣታችሁ በታሪክ ተመዝግቦ ለትውልድ እንደሚተላለፍም ተስፋ እናደርጋለን።ችሎቱ ነገም ጥቅምት 10 ቀን 2014 ዓ.ም. More/ተጨማሪ…

ዐቃቤ ሕግ በእነ እስክንድ ነጋ ላይ የሚቀርቡ ምስክሮች ዝርዝር በሚዲያ እንዳይቀርብ ያቀረበውን አቤቱታ ፍ/ቤት ውድቅ አድርጎታል
በዚህም መሰረት ፦በነ #እስክንድር ነጋ ላይ ከነገ ጥቅምት 10 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ በግልፅ ችሎት እንዲመሰክሩ ዐቃቤ ሕግ የዘረዘራቸው ሰዎች ስም ዝርዝር:-1. ፈንታሁን አሰፋ2. መንበረ በቀለ3. ወርቁ ታደሰ4. ፍፁም ተሰማ5. ደረጀ ግዛው6. ቴዎድሮስ ለማ7. ያየህ ብርሃኑ8.ጌትነት ተስፋዬ9. ትንሳኤ ማሞቀሪ የ12 ምስክሮች ስም ዝርዝር ነገ ጧት እንዲቀርብ ታዝዟል። ከላይ ከተጠቀሱት መካከል ሁለቱ ነገ ምስክርነታቸውን ይሰጣሉ ተብሎ More/ተጨማሪ…