ባልደራስ Balderas logo
  • ዋና ገጽ
  • ዜና
  • ጋዜጣዊ መግለጫ
  • ፖ/ፕሮግራም
  • ምርጫ 2013
  • ባልደራስ ጋዜጣ
  • አባል ይሁኑ

About Us | Contact Us | Sitemap |
December 22, 2022

የግፍ እስረኛው አቶ ካሳሁን ለይደር ተቀጠሩ

የግፍ እስረኛው አቶ ካሳሁን ለይደር ተቀጠሩ
 
በሀሰት ክስ ለታሰሩት አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ ስንቅ ለማቀበል እና ለመጠየቅ በሄዱበት በፖሊስ ታግተው እዛው የቀሩት አቶ ካሳሁን ደስታ ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ በቀጠሯቸው መሰረት ፍ/ቤት ቀርበዋል።
ፓሊስ በዛሬው ችሎት ላይ አቶ ካሳሁን ሌላውን እስረኛ አቶ ናትናኤልን ለመጠየቅ በሄዱበት እንዳሰራቸው ክዷል። ይባስ ብሎም አቶ ካሳሁንን ያሰረበትን ምክንያት ሲናገር ”በአምሀ ደስታ ት/ቤት በነበረው ተቃውሞ ላይ ከኋላ መኪና ይዘው ሲያስረብሹ ነበር” ብሏል። ጠበቃቸው ጠበቃ ሄኖክ አክሊሉ በበኩላቸው ደምበኛቸው መኪናም ሆነ መንጃ ፍቃድ እንደሌላቸው እና ማሽከርከርም እንደማይችሉ አስረድተዋል። ይህ ሀሰተኛ የፖሊስ ክስም እንዲመዘገብላቸው ጠይቀዋል።
ፖሊስ የሰነድ እና የሰው ምስክር ለማደራጀት እና ያልተያዙ ግብረአብሮችንም ለመያዝ ተጨማሪ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ጠይቋል። የግፍ እስረኛው ጠበቃም ክሱ ፍፁም ሀሰት መሆኑን በመግለፅ፣ እስረኛው እስካሁን የቆዩበት 10 ቀናት ለምርመራ በቂ በመሆኑ ፖሊስ የጠየቀው 14 ቀን መፈቀድ የለበትም ብለዋል። በመሆኑም ፍርድ ቤቱ የፖሊስን ጥያቄ ውድቅ አድርጎ የተከሳሹ የዋስትና መብት እንዲከበር ጠይቀዋል። በተጨማሪም የፖሊስ መዝገብ ቀርቦ እንዲታይ ጠይቀዋል።
 
ፍርድ ቤቱም ግራ ቀኙን ከሰማ በኋላ መዝገቡን መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት በይደር ለነገ አርብ (14/04/2015 ዓ.ም) ለጠዋት 3:30 ቀጥሯል።
በነገው እለት ሁለቱም በግፍ እስር ላይ የሚገኙት የባልደራስ ንቁ-አባላት አቶ ካሳሁን ደስታ እና አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ በአራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት የሚቀርቡ ይሆናል።
ፍትህ ለግፍ እስረኞች!
ድል ለዲሞክራሲ!
የግፍ እስረኞቹ አቶ ካሳሁን ደስታ እና አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ ነገ እና ከነገ ወዲያ ፍ/ቤት ይቀርባሉ ሁለቱም የግፍ እስረኞች ለ ታህሳስ 19 ተቀጠሩ

Related Posts

ሁለቱም የግፍ እስረኞች ለ ታህሳስ 19 ተቀጠሩ

ዜና

ሁለቱም የግፍ እስረኞች ለ ታህሳስ 19 ተቀጠሩ

ዜና

የግፍ እስረኞቹ አቶ ካሳሁን ደስታ እና አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ ነገ እና ከነገ ወዲያ ፍ/ቤት ይቀርባሉ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ ዞን ሚዢጋ ወረዳ ታንካራ ቀበሌ በኦሮሚያ ልዩ ኃይል ከተገደሉት ንፁሃን መካከል የሰባቱ ሰዎች አስከሬን ስርዓተ ቀብር ተፈፀመ

ዜና

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ ዞን ሚዢጋ ወረዳ ታንካራ ቀበሌ በኦሮሚያ ልዩ ኃይል ከተገደሉት ንፁሃን መካከል የሰባቱ ሰዎች አስከሬን ስርዓተ ቀብር ተፈፀመ

Recent Posts

  • ሁለቱም የግፍ እስረኞች ለ ታህሳስ 19 ተቀጠሩ December 26, 2022
ባልደራስ Balderas logo
  • ዋና ገጽ
  • ዜና
  • ጋዜጣዊ መግለጫ
  • ፖ/ፕሮግራም
  • ምርጫ 2013
  • ባልደራስ ጋዜጣ
  • አባል ይሁኑ

ድል ለዲሞክራሲ!!!

© ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ Balderas for true democracy 2021