“ፍትሕ ለግፍ እስረኞች ” የማህበራዊ ድረ-ገፅ ዘመቻ!

በመከራና እንግልት ያልተበገረው ደፋሩና ጀግናው ውድ የኢትዮጵያ ልጅ እስክንድር ነጋ ይፈታ!!!
የወታደራዊ አስተዳደር ደርግ መንግሥት በ1960ዎቹ መጨረሻ አካባቢ በእስክንድር ነጋ ወላጆች ላይ የተለያዩ በደሎች በማድረሱ ጨቅላውን እስክንድርን ይዘው ወደአሜሪካ ተጓዙ፡፡ እስክንድር በአሜሪካ በቆየበት ወቅት ኢትዮጵያውያን የደርግን መንግሥት በመቃወም ሰላማዊ ሰልፎች ሲያካሂዱ እሱም በዚያ በለጋ የተማሪነት ዘመኑ ሰላማዊ ትግሉን ተቀላቅሎ የበኩሉን አስተዋጽኦ አበርክቷል፡፡የደርግ መንግሥት ወድቆ ሕወሀት ወደ ሥልጣን ከመጣ በኋላ፣ እስክንድር ነጋ በ1985 ዓ.ም. ወደ ሀገርቤት ተመለሰ። More/ተጨማሪ…

” የባልደራስ አመራሮች ባስቸኳይ ሊፈቱ ይገባል! “
የባልደራስ ሊቀመንበር እስክንድር ነጋን ጨምሮ ስንታየሁ ቸኮል፣ አስቴር ስዩም፣ አስካለ ደምሌ የታሰሩት፣ የሀጫሉን ግድያ ተከትሎ ብዙ ወንጀል እንዲሰራ ላደረጉት ሌሎች አካላት ማመጣጠኛ ነው። እነ እስክንድር ምንም ሳያደርጉ ታስረው ብዙ ወንጀል የሰሩ ግን አሁንም የሽግርር መንግስት በማቋቋም ላይ ናቸው። ዋናው ነገር እነ እስክንድር ምንም አይነት ወንጀል አልሰሩም ነው። ብዙ ንፁሃንን አስፈጅተው ለታሰሩት ማመጣጠኛ ተብለው የታሰሩት እነ More/ተጨማሪ…

እስክንድር ነጋ ማን ነው ?!
እስክንድር ነጋ ፈንታ በ1960 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተወለደ። አባቱ የአሜሪካው ሩትጋርት ዩኒቨርሲቲ ባልደረባ ሲሆኑ እናቱ ደግሞ የአሜሪካ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቤሩት አስተማሪ ነበሩ። በኋላም በአዲስ አበባ የግል የጤና ተቋም አቋቁመው በመንግሥት ንብረቶቻቸው እስከወረሰባቸውና ሥራቸውን እስካስቆመበት ጊዜ ድረስ ሀገራቸውን በብዙ አገልግለዋል። እስክንድር እድሜው ለትምህርት ሲደርስ አዲስ አበባ በሚገኘው ሳንፎርድ ኢንግሊሽ ስኩል መማር ጀመረ። ትምህርት ቤቱ የተሻለ የትምህርት More/ተጨማሪ…
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ “የፈራ ይመለስ” መፅሐፉ ላይ እስክንድር ነጋን እንዲህ ሲል ገልፆታል።
“እስክንድር ነጋ ለእኔ ከነ አሉላ አባ ነጋ፣ከእነ ዘረዓይ ደረስ፣ ከነ አብዲሳ አጋ ትይዩ የሚቆም የአገር ባለውለታ ጀግና ነው። “
”የያዝኩትን መሬት ኢትዮጵያዬን እንዳልለቅ የመንፈስ ብርታት የሆነኝም ይህ ሰው ነው።”
https://www.facebook.com/Balderas.Ethio/photos/a.103738714595344/482835816685630/?type=3&eid=ARBksvkYg7qcg-863YCkyn_7FnaZ0rBcGghJjzcpr2uImiUa57luD-2tCqJsKKpivvaOG25g-wVaHEK8&__xts__%5B0%5D=68.ARB_cVCj-XaYkJfJGj0WrRut8BSz_rxVbyXwBvEYDXhxCQx_g3rELsGNdwrRys8hzzu5ZcOoio2HFauPGWNUYMzCMIEdX2UhACEEZYjXazz7cZTxT_JPXsZHwtIwBUDkYKSte2i7gBuWlHNH_mUTuJyibq1kz-_b0L_rSZFa2-ZuhgOGLBE07aN11faIWYds5IbHpoIpkYk_-yD-hMRiodFwaWThzGGqeITqKftf4OEMMCTCjINafMtEez9H-JSHjtCHYy4CLoP-K91gglfsil_OKcnufUeJByFsYGffJ0kMYqlWm-U&__tn__=EHH-R
ዜና

በጋዜጠኛ ጌጥዬ ያለው እስር ላይ ሦስት ወር ተቀነሰ !
የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጋዜጠኛ ጌጥዬ ያለውን ችሎት በመድፈር ጥፋተኛ በማለት በ4 ወር እስራት እንዲቀጣ መወሰኑ የሚታወስ ነው ።ሆኖም ፤ ከፍተኛው ፍርድ ቤት የሰጠው የቅጣት ውሳኔ ውድቅ እንዲሆን በቀረበው ይግባኝ መሠረት ፤ይግባኙን የመረመረው ጠቅላይ ፍ/ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎች በከፍተኛው ፍርድ ቤት የተሰጠውን የቅጣት ውሳኔ ሦስት ወር በመቀነስ በአንድ ወር እስራት ውሳኔ ሰጥቷል ።

እነ እስክንድር ነጋ በተከሰሱበት መዝገብ ጋዜጠኛ ጌጥዬ ያለው ታሰረ ! የምስክር አሰማም ሂደት ለጥቅምት ተቀጠረ !
በእነ እስክንድር የክስ መዝገብ ፤ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጸረ ሽብርና ሕገ መንግሥት ጉዳዮች ወንጀል ችሎት፤ ከችሎት ዘገባ ጋር በተያያዘ ጠበቃ ቤተማርያም አለማየሁ ፣ ጋዜጠኛ ጌጥዬ ያለው እንዲሁም አሐዱ ራዲዮ ” የተሳሳተ እና ዘገባ እና ጽሁፍ ” በማቅረቡ እና ችሎት መድፈር ህግ ተላልፋችኋል በማለት ከፍተኛ ፍርድ ቤት በፖሊስ በላከው መጥሪያ መሰረት ተጠርጣሪዎች ዛሬ ፍ/ቤት ቀርበዋል።ፍ/ቤቱ More/ተጨማሪ…
ሰበር ሰሚ ችሎቱ በእነ እስክንድር ነጋ ዶሴ ላይ ለነሐሴ 10 ቀን 2013 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ
የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በእነ እስክንድር ነጋ መዝገብ ላይ ተለዋጭ ቀጠሮ የሰጠው ‘የዐቃቤ ሕግ ምስክሮች ከመጋረጃ ጀርባና በዝግ ችሎት ይቅረቡ ወይስ በግልፅ ችሎት ይሰሙ’ ለሚለው ክርክር ብይን ለመስጠት ነው። ትናንት ነሐሴ 3 ቀን 2013 ዓ.ም. በነበረው ችሎት መዝገቡን አለመመርመሩን ጠቅሶ ለዛሬ ነሐሴ 4 ቀን 2013 ዓ.ም. ማሸጋገሩ ይታወሳል።ይህንኑ የምስክሮች አሰማም ሂደት በተመለከተ More/ተጨማሪ…
ጋዜጣዊ መግለጫ
ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን የማፍረስ ዘመቻ ይቁም!
ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ (ባልደራስ) በአፋር አርብቶ አደር ወገኖቻችን ላይ በተፈፀመው ግድያ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል። ለሟች ቤተሰቦችና ለመላው የአፋር ብሎም የኢትዮጵያ ሕዝብ መፅናናትን ይመኛል። ኦሕዴድ/ብልፅግና ኢትዮጵያን ከቻለ አፍርሶ በራሱ ቀለም እንደገና ለመሥራት ይህ ካዳገተውም እንደ ሐረሩ የራስ መኮንን ሀውልት አፈራርሶ ለመተው እየተንቀሳቀሰ እንደሆነ እናምናለን። ቅርሶችን ጨምሮ ነባር የኢትዮጵያ መገለጫዎችን የማፍረስ እና አንዳዶችን በአዲስ የመተካት More/ተጨማሪ…

ባልደራስ ሊያካሂደው የነበረውን የምርጫ ቅስቀሳ ሰረዘ !!
ባልደራስ ሊያካሂደው የነበረውን የምርጫ ቅስቀሳ ሰረዘ !!ከሁሉ አስቀድመን በአገራችን በኦሮምያ ክፍለ-ሃገር በተለያየ ወቅት በተደጋጋሚ በተፈጸመ ጥቃት ፤ በንጹሃን ዜጎች በኦህዴድ/ብልጽግና ይሁንታ እና ኦነግ ሸኔ በተባለ የዳቦ ስም የተሰጠው ገዳይ ቡድን አድራጊነት የዘር ማጥፋት ወንጀል ሰለባ ለሆኑ የተሰማውን ጥልቅ ኃዘን ባልደራስ እውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ይገልጻል!የሟቾችን ነፍስ ፈጣሪ በአጸደ ገነት ያኑርልን፡፡ ለውድ ቤተሰቦቻቸው እና ወዳጆቻቸው መጽናናትን እንመኛለን፡፡በንጹሃን More/ተጨማሪ…
መጣጥፍ – ነፃ አስተያየት
የኢትዮ ቴሌኮም ሽያጭ ጥቅምና ጉዳት ጉዳይ ሙያዊ ቅኝት (ሳመንጉሥ ጥላሁን)
አፄ ምኒሊክና የመጀመሪያው የስልክ ግንኙነት ኢትዮጵያ፣በ1886ዓ.ም፣በታላቁ ንጉሠ ነገሥት አፄ ምኒሊክ ዘመነ መንግሥት፣ የመጀመሪያውን የ477 ኪ.ሜ የስልክ መሥመር ዘርግታ፣“ጤና ይስጥልኝ ዐዲስ!! ጤና ይስጥልኝ ሐረር!!” ካስባለች፣126 ዓመታት ተቆጠሩ። አፄ ምኒሊክ፣ሀገሪቷን ያስተዳድሩ በነበሩበት ዘመን ያስገቧቸውን፣ዘመናዊ አሠራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን ብዛት ስናይ፣አፄ ምኒሊክ፣“የሥልጣኔ ማግኔት ነበሩ!!” ለማለት እንችላለን። አፄ ኃይለሥላሴና የቴሌኮሙኒኬሽን እድገት ኹኔታ የቴሌፎን ቴክኖሎጂ ወደ ኢትጵያ የገባው፣በ1886 ዓ.ም በምኒልክ More/ተጨማሪ…
ዘር ማጥፋት ወይስ ሰብዓዊ ፍጡር ላይ የተፈጸመ ወንጀል?
እስክንድር ነጋ፣ የህሊና እስረኛ፤ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት፣ አዲስ አበባከሁሉ አስቀድሞ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ከሀጫሉ ግድያ በኋላ በኦሮሚያ ክልል ስለተከሰተው ሁኔታ ያወጣው ሪፖርት ምሥጋና ይገባዋል፡፡ የሚንቀሳቀስበትን አውድ ግምት ውስጥ እናስገባለት፡፡ ያለው ኢትዮጵያ ውስጥ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ብዙ በጐ እሴቶች ያሏት ሀገር መሆኗ የሚካድ ባይሆንም፣ በሰብዓዊ መብት አክባሪነታቸው ከሚወደሱ ሀገራት ተርታ ለመሰለፍ ግን አልታደለችም፡፡ በፍጥነት የሚበቅልና የሚለመልም More/ተጨማሪ…
ውስጠ ወይራው ያለመለወጥ ‹ለውጥ› (፪)
በክፍል አንድ መጣጥፌ ‹ለውጥ› እየተባለ የሚወራው ሀሰት መሆኑን አብራርቻለሁ፡፡ ‹ለውጥ› ተብየው ውስጠ ወይራ እንደሆነ እና ‹የለውጡ› መሪ ነኝ ባዩ አብይ አሕመድ ነብረው የወጡት ወያኔ የጣለውን እንቁላል እንደሆነ አብራርቻለሁ፡፡ በ‹ለውጥ› ሽፋን ‹ለውጥን› የመከላከል ቁልቁለቱ አያሌ ርዕዮተ ዓለማዊ፣ ሕገ መንግሥታዊ፣ ተቋማዊ እና ሥርዓታዊ መገለጫዎች አሉ፡፡ ከእነዚህም መካከል ሦስት መገለጫዎችን ቀንጭቤ እገልፃለሁ፡፡ አንደኛው የአዳፍኔነትና የአስቀጣይነት መንታ ስለት ሲሆን More/ተጨማሪ…