ባልደራስ Balderas logo
  • ዋና ገጽ
  • ዜና
  • ጋዜጣዊ መግለጫ
  • ፖ/ፕሮግራም
  • ምርጫ 2013
  • ባልደራስ ጋዜጣ
  • አባል ይሁኑ

About Us | Contact Us | Sitemap |
June 11, 2021

የሐዘን መግለጫ

የአንጋፋውን የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ሊቅ፣ የፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌን ሕልፈተ ሕይወት የሰማነው፣ በጥልቅ የሐዘን ስሜት ነው፡፡ ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ፣የኢትዮጵያ፡ቁዋንቁዎችንና ፡ሥነጽሑፍ እንዲኹም ታሪክ አስመልክተው ፣አያሌ የጥናትና የምርምር መጻሕፍትን ያበረከቱ ብርቅ፡ኢትዮጵያዊ፡ምሁር፡ነበሩ።
የቋንቋ ፣የሥነ ጽሑፍ፣የታሪክና የሥነመለኮት ሊቁ ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ፣ በተለያዩ አገራዊና አህጉራዊ የፖለቲካ እድገት አስተዳደርና ዴሞክራሲያዊ ነክ ጉዳዮች ላይ ይሰጡዋቸው፡በነበሩቱ በሳል ሀሳቦቻቸው እና ትችቶቻቸው ይታወቁ፡ነበር።

እኚህ ሀገራቸውን ወዳድ፣ ዓለም አቀፋዊ ምሁር ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ፣ የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ
አማካሪ ምክር ቤት አባላት መካካል አንዱ በመሆን፣ ለፖርቲያችን ያበረከቱት አስተዋጽዖ እጅግ የጎላ ነበር ። ለዚህም አኩሪ ተግባራቸው፣ ፓርቲያችንና ታሪክ፣ኹሌም ስማቸውን በክብር ሲያወሳ ይኖራል። ስለኾነም፣ የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ፣ በመላው የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎቹ ስም፣በፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ሕይወት ማለፍ የተሰማውን ልባዊ ሐዘን እየገለጸ፣ለነፍሳቸው እረፍትን፣ ለቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው ደግሞ የልብ፡መፅናናትን ይመኛል።

የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ

ለ1997 ዓ.ም. ሰማዕታት ቋሚ መታሰቢያ ይቁምላቸው! አስቻይ ሁኔታዎች በሌሉበት የሚከናወን ምርጫ ሀገር በጉጉት ወደምትጠብቀው ሥርዓት አያሸጋግርም !

Related Posts

ጋዜጣዊ መግለጫ

የወቅቱን የሃገራችንን የፖለቲካ እና ወታደራዊ ሁኔታ በማስመልከት ከባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ !

” የምርጫ ውጤቱ ተቀባይነት የለውም። ድምፅ ተዘርፏል”

ጋዜጣዊ መግለጫ

” የምርጫ ውጤቱ ተቀባይነት የለውም። ድምፅ ተዘርፏል”

ጋዜጣዊ መግለጫ

በምርጫው ጉዳይ ላይ ከባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ !

Recent Posts

  • የባልደራስ ድጋፍ ሰጪ በሰሜን አሜሪካ October 23, 2021
ባልደራስ Balderas logo
  • ዋና ገጽ
  • ዜና
  • ጋዜጣዊ መግለጫ
  • ፖ/ፕሮግራም
  • ምርጫ 2013
  • ባልደራስ ጋዜጣ
  • አባል ይሁኑ

ድል ለዲሞክራሲ!!!

© ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ Balderas for true democracy 2021