ዜና(News)
ለባልደራስ ክስ ምርጫ ቦርድ ነገ በፍርድ ቤት መልስ ያቀርባል !
ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ (ባልደራስ) ምርጫ 2013 ላይ የተሠሩ ሕገ ወጥ ተግባራትን በተመለከተ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቅሬታዎችን ቢያቀርብም ከሕግ አግባብ ውጭ በማን አለብኝነት ውድቅ ተደርገውበታል። በመሆኑም ጉዳዩን ወደ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወስዶ በምርጫ ቦርድ ላይ ሕጋዊ ክስ መስርቷል።ፓርቲው ለመሰረተው ሕጋዊ ክስ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነገ ሀምሌ 23 ቀን 2013 ዓ.ም. ለፍርድ ቤቱ More/ተጨማሪ…
አስቸኳይ ማስተካከያ !
ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ (ባልደራስ) የ2013 ዓ.ም. ምርጫን አጠቃላይ የጥናት/የምርመራ ውጤት አስመልክቶ ነገ ሐምሌ 23 ቀን 2013 ዓ.ም. በራስ አምባ ሆቴል ረፋድ 4፡00 ሰዓት ይፋ ለማድረግ ለመገናኛ ብዙኅን ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል።ይሁን እንጂ ባልደራስ ሊሰጠዉ ያቀደው ጋዜጣዊ መግለጫ በመንግስት አፋኝ ቡድን በመከልከሉ ጥናቱን በተጣበበ ቦታም ቢሆን በቢሯችን ይፋ ለማድረግ ወስነናል።በመሆኑም በተጠቀሰው ሰዓት ስድስት ኪሎ፤ ምስካየኅዙናን መድሀኒያለም More/ተጨማሪ…
የጋዜጣዊ መግለጫ ጥሪ
የሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ/ም የተደረገውን ምርጫ በተመለከተ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኩል አጠቃላይ ውጤት መገለጹ የሚታወቅ ነው።ይህም በመሆኑ የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የ2013ን ምርጫ አጠቃላይ የጥናት/የምርመራ ውጤት አስመልክቶ ነገ ሐምሌ 23 ቀን 2013 ዓ.ም በራሳ አምባ ሆቴል ጠዋት 4፡00 ሰዓት ይፋ ያደርጋል ። የእለቱን መርሃግብር የሚዲያ ሽፋን እንድትሰጡ ስንል ጥሪ እናቀርባለን ።ከሠላምታ ጋር !
ከፍተኛ ፍ/ቤቱ ለሃምሌ 29 እነ እስክንድርን በድጋሜ ቀጠረ
አቃቤ ሕግ ከጠቅላይ ሰበር ሰሚ ችሎት ያወጣውን የዕግድ ትዕዛዝ ማህተም አስደርጎ ለ9 ሰዓት “ቀርቢያለሁ” ማለቱን ተከትሎ ነው በድጋሜ ለሐምሌ 29 ቀን 2013 ዓ.ም የተቀጠረው።የፌደራሉ ጠቅላይ ሰበር ሰሚ ችሎት ባወጣው የዕግድ ትዕዛዝ ዙሪያ ሐምሌ 26 /2013 ዓ.ም የግራ ቀኙን ጉዳይ ለመመልከት ቀጠሮ ሰጥቷል።ከፍተኛ ፍ/ቤቱ አቃቤ ሕግ በግልፅ ችሎት በአምስት ቀናት ውስጥ ምስክር እንዲያሰማ ትዕዛዝ መስጠቱ ይታወሳል። More/ተጨማሪ…