ባልደራስ Balderas logo
  • ዋና ገጽ
  • ዜና
  • ጋዜጣዊ መግለጫ
  • ፖ/ፕሮግራም
  • ምርጫ 2013
  • ባልደራስ ጋዜጣ
  • አባል ይሁኑ

About Us | Contact Us | Sitemap |
June 3, 2021

ምርጫ ቦርድ እነ እስክንድር ነጋን በዕጩነት ሊመዘግብ ነው !

ምርጫ ቦርድ እነ እስክንድር ነጋን በዕጩነት ሊመዘግብ ነው !

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በወሰነው መሰረት በግፍ እስር ላይ የሚገኙት የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ መሪዎች እስክንድር ነጋ፣ ስንታየሁ ቸኮል፣ አስቴር ስዩም እና አስካለ ደምሌ በመጭው ምርጫ በዕጩ ተወዳዳሪነት እንዲቀርቡ ለማድረግ ሥራዎችን መጀመሩን አስታውቋል። የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ግንቦት 26 ቀን 2013 ዓ.ም. የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ የምርጫ ጉዳዮች ችሎት ቀርዋል።

ቦርዱ የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ እንደሚፈፅምም ተናግረዋል። የዕጩዎቹን ስም ዝርዝር እና በእነ ማን እንደሚተኩ ለቦርዱ ያቀረበው ባልደራስ ለእነ እስክንድር ነጋ የዕጩነት ማረጋገጫ ሰነድ እንዲሰጠው መጠየቁን የፓርቲው የሕግና ሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ሓላፊ ጠበቃ ሔኖክ አክሊሉ ተናግረዋል። ምርጫ ቦርድ ቀሪ ሥራዎችን አጠናቆ ሰነዱን ግንቦት 30 ቀን 2013 ዓ.ም. በፍርድ ቤቱ ፊት እንዲያቀርብም ቀጠሮ ተይዟል።

እንደ ቦርዱ ማብራሪያ ዕጩዎቹን ለማተካካት በተደረገው እንቅስቃሴ ታትሞ የነበረ 1.3 ሚሊዮን ወረቀት ተወግዷል። በዚህም ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ ወጭ ተደርጓል።

እነ እስክንድር በእጩነት እንዳይመዘገቡ የሚከለከሉበት ህጋዊ ምክንያት የለም ! መምህር ተሰማ አያሌው

Related Posts

ዜና, የማህበራዊ ድረ-ገፅ ዘመቻ

የባልደራስ ድጋፍ ሰጪ በሰሜን አሜሪካ

ህመሙ _አመመኝ

ዜና, የማህበራዊ ድረ-ገፅ ዘመቻ

ህመሙ _አመመኝ

የእስክንድር እግር መሰበሩ በህክምና ተረጋገጠ !

ዜና, የማህበራዊ ድረ-ገፅ ዘመቻ

የእስክንድር እግር መሰበሩ በህክምና ተረጋገጠ !

Recent Posts

  • የባልደራስ ድጋፍ ሰጪ በሰሜን አሜሪካ October 23, 2021
ባልደራስ Balderas logo
  • ዋና ገጽ
  • ዜና
  • ጋዜጣዊ መግለጫ
  • ፖ/ፕሮግራም
  • ምርጫ 2013
  • ባልደራስ ጋዜጣ
  • አባል ይሁኑ

ድል ለዲሞክራሲ!!!

© ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ Balderas for true democracy 2021