ባልደራስ Balderas logo
  • ዋና ገጽ
  • ዜና
  • ጋዜጣዊ መግለጫ
  • ፖ/ፕሮግራም
  • ምርጫ 2013
  • ባልደራስ ጋዜጣ
  • አባል ይሁኑ

About Us | Contact Us | Sitemap |
October 23, 2021

ህመሙ _አመመኝ

ህመሙ _አመመኝ

 

አቶ ስንታየሁ ቸኮል የኅሊና እስረኛ ከቂሊንጦ

እስክንድር ነጋ የድርጅቴ መሪ ራስ ነው!
ለኔ ደግሞ የሥራ አለቃዬ ነው!
እስክንድር ታላቅ ወንድሜ መካሪዬ ነው።
እስክንድር ለጋራ መስዋዕትነት የተጠራን የቁርጥ ቀን የሀገሬ ሕብረ_ቀለም ሃቀኛ ጓዴ ነው።

ከመሪዬ ጋር በአንድ ቤት ውስጥ ሆነን በተቀራረበ መኝታ ላይ እንዴት እንዳዳረ አውቃለሁ። ህመሙ- አመመኝ… ላብ በሚያጠምቅ ምጥ ..እእእእእ… የጥዝጣዜ ስሜት ቦታው ላይ መፍትሄ አጥተህ መጋራት ከባድ ነው። ቁጭት የተቀላቀለበት ህመም ብስጭት መራር ሀዘን ብቻ ያሳዝናል።

ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን 2014 ዓ,ም ጠዋት 1:00 ሰዓት ላይ እስክንድር እንደወትሮው ወደ ውጭ እያነከሰ ወጣ እንዴት እንዳደረ ስሜቱን አውቃለሁ፤ “ለምን ትወጣለህ ተኛ እንጅ እስክንድር” አልኩት። ለሊቱን ሙሉ እንዳልተኛ እና እግሩ በጣም እንዳመመው ነገረኝ። ይህን እኔም ስለሰማሁት ወዲያው በሙቅ ውሃ ለማሸት ሞከርኩ ግን ብዙም አልተቻለም። እጅግ የከፋ ህመሙ ተሰምቶት ነበር። በአስቸኳይ ወደ እክምና እንዲሄድ ለተረኛ ፖሊስ መኮንን ተናገረ.. ወደ ፖሊስ በመሄድ የእስክንድር እግር መሰበሩ በህክምና ተነገረው ።

በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በሥርዓቱ ዕቅድና ተልዕኮ የተደበደበው እስክንድር ነጋ፣ ዛሬ ከሰዓት ቦኃላ በፖሊስ ሆስፒታል በተደረገለት ህክምና ፣ በግራ እግሩ ላይ አውራ ጣቱ መሰበሩ በራጂ ታውቋል።

በዚህም መሠረት፣ ለሚቀጥሉት ስድስት ሳምንታት የሚቆይ ጄሶ ተደርጎለታል እንደሚቆይ ተነግሮታል።

ጠንካራው መሪያችን እስክንድር ነጋ ከማረሚያ ቤት ሆኖ ያስተላለፈው መልዕክት፣ ስሜት ቀስቃሽ ወኔ የሚጠግን ነበር።

“…በሰሜን ያለውን ጦርነት አስባለሁ። የታሰሩትን አባሎቻችንን አስባለሁ። አጥንታችንን መስበር ይቻላል። ትግላችንን ግን መስበር አይቻልም ” ብሏል።

ወኔ ያለው አመራር ይህ ነው። እስክንድር ነፍሱ ለእውነት የተጠራች ጀግና ታጋይ ነው። አምላኩን ሁሌም የማይረሳ በችግር ላይ ሆኖ ስለፍቅር ይቅርታ የሚሰብክ ደቀመዝሙር ነው።

የኛን ችሎት ለመታደም የመጡ የባልደራስ ፈርጦቻችን እናተ በርቱዎች በመስዋዕትነታችሁ ኮርተናል በመከራችሁ ብናዝንም ይህ እስራችሁ ግን ተመንዝሮ ህዝብ ይከፍላችዋል። ታሪክ ይክሳችዋል! ስለእኛ ዋጋ የምትከፍሉ ስለሀገራችሁ መፃሂ ዕድል ዛሬ በቆራጥ ትግል ያላችሁ ጓዶች ሁሉ እመነኙ ህዝብ አይረሳችሁም ከዚች ጠባብ እስር ቤት ሆነን እናስባችዋለን እናከብራችዋለን።

ድል ህዝባችን!
ድል ለሃቀኛ ታጋዮች!

የእስክንድር እግር መሰበሩ በህክምና ተረጋገጠ ! የባልደራስ ድጋፍ ሰጪ በሰሜን አሜሪካ

Related Posts

ሁለቱም የግፍ እስረኞች ለ ታህሳስ 19 ተቀጠሩ

ዜና

ሁለቱም የግፍ እስረኞች ለ ታህሳስ 19 ተቀጠሩ

የግፍ እስረኛው አቶ ካሳሁን ለይደር ተቀጠሩ

ዜና

የግፍ እስረኛው አቶ ካሳሁን ለይደር ተቀጠሩ

ዜና

የግፍ እስረኞቹ አቶ ካሳሁን ደስታ እና አቶ ናትናኤል ያለምዘውድ ነገ እና ከነገ ወዲያ ፍ/ቤት ይቀርባሉ

Recent Posts

  • ሁለቱም የግፍ እስረኞች ለ ታህሳስ 19 ተቀጠሩ December 26, 2022
ባልደራስ Balderas logo
  • ዋና ገጽ
  • ዜና
  • ጋዜጣዊ መግለጫ
  • ፖ/ፕሮግራም
  • ምርጫ 2013
  • ባልደራስ ጋዜጣ
  • አባል ይሁኑ

ድል ለዲሞክራሲ!!!

© ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ Balderas for true democracy 2021